<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://www.v1.bornatol.com/feed/am</id>
                                <link href="https://www.v1.bornatol.com/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(http://v1.bornatol.com) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-07-01T15:50:00+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[የኢቪ (EV) መሠረተ ልማት ግንባታና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ቁርጠኝነት]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/publication/detail/2400?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/2400</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image image-style-align-left"><img src="/lfm/1782910162.jpg"></figure><p>&nbsp;</p><p>&nbsp;<br>ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን በመጠቀም የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት በአፍሪካ ደረጃ በምሳሌነት የሚጠቀስ ሆኗል። ሀገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ከቀረጸቻቸው ስትራቴጂዎች መካከል አንዱና ዋነኛው የትራንስፖርት ዘርፉን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል (EV) ማሸጋገር ነው።<br>&nbsp;<br>ለአካባቢ ጥበቃ ከሚኖረው የማይተካ ሚና ባሻገር፣ በነዳጅ ግዢ ላይ የሚባክነውን እጅግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማስቀረት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ የተወሰደው የመንግስት ውሳኔ ፍሬ ማፍራት ከጀመረ ሰንበትበት ብሏል። ይህ ታላቅ ሀገራዊ አላማ ግን ያለ ጠንካራ መሠረተ ልማት ብቻውን ግቡን ሊመታ አይችልም። የተሽከርካሪዎችን መበራከት ተከትሎ የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን (Charging Stations) በበቂ ሁኔታ መገንባት የሽግግሩ ስኬት ወሳኝ ምሰሶ ሆኖ ቀርቧል።<br>&nbsp;<br>እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ወደ 140 ሺህ የሚጠጉ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ቢሆንም፣ ከተሽከርካሪዎቹ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን የኃይል መሙያ ጣቢያዎች አለመሟላት ለተጠቃሚዎች ዋነኛ ፈተና ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ክፍተት ለመሙላትና የተጠቃሚዎችን መጉላላት ለመቅረፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (EEU) ልዩ ትኩረት በመስጠት በከፍተኛ ፍጥነትና መዋዕለ ንዋይ ወደ ስራ ገብቷል። ተቋሙ በመጀመሪያው ምዕራፍ እቅዱ በአዲስ አበባ 32፣ እንዲሁም በሌሎች የክልል ከተሞች 8 በድምሩ 40 የቻርጂንግ ስቴሽኖችን ለመገንባት ቆርጦ ተነስቷል።<br>&nbsp;<br>በዚህም መሰረት ባለፈው መጋቢት ወር በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ተገንብተው ስራ የጀመሩት የኮተቤ (በሳአሊተ ምህረት ፊት ለፊት)፣ የለቡ እና የፒያሳ (በቀድሞው የአገልግሎቱ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ) የኃይል መሙያ ጣቢያዎች ለተጠቃሚዎች ክፍት መደረጋቸው ይታወሳል።<br>&nbsp;<br>ተቋሙ የጀመረውን የማስፋፋት ስራ ይበልጥ አጠናክሮ በመቀጠል በቅርቡ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር አዲስ የኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን አስመርቆ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አራት ዘመናዊ ጣቢያዎች አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ሁለት ጣቢያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝግጁ ይሆናሉ።<br>&nbsp;<br>የኃይል መሙያ ጣቢያዎች መገንባታቸውና አገልግሎት መስጠታቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የገነባቸው ጣቢያዎች በሙሉ የ24 ሰዓት ሙሉ አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸው ለተጠቃሚዎች ትልቅ እፎይታ ነው። ከዚህ በተጨማሪም፣ የተቋሙን የኤሌክትሪክ መስመሮች ጫና ለመቀነስና የህዝቡን የኃይል አጠቃቀም ባህል ለማሻሻል ሲባል በጊዜ ላይ የተመሰረተ ምክንያታዊና ተለዋዋጭ የዋጋ ተመን ተዘጋጅቷል።<br>&nbsp;<br>የዋጋ ተመኑ፤ ከምሽቱ 4:00 እስከ ጠዋት 12:00 ሰዓት (Off-Peak)፦ ለአንድ ኪሎ ዋት (kWh) 14.85 ብር። ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 11:00 ሰዓት &nbsp;ለአንድ ኪሎ ዋት 16.57 ብር። ከቀኑ 11:00 እስከ ምሽቱ 4:00 እና ከጠዋቱ 12:00 እስከ 4:00 (Peak Hours)፦ ለአንድ ኪሎ ዋት 18.28 ብር ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። ይህ አሰራር ተጠቃሚዎች በሌሊት ቻርጅ በማድረግ ወጪያቸውን እንዲቆጥቡ ከማስቻሉም በላይ፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈጠርን ከፍተኛ ጫና ይቀንሳል።<br>&nbsp;<br>ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የወደፊት እቅዶችና ቀጣይ ስራዎችም ተስፋ ሰጪ ናቸው። ተቋሙ አገልግሎቱን በዋና ከተማዋ ብቻ ሳይወሰን በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ወደ ክልል ከተሞች ለማስፋፋት በዝግጅት ላይ ይገኛል። በዚህም መሰረት በቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ ባቱ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ እና ሐዋሳ ከተሞች ላይ አዳዲስ የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት እቅድ ይዟል። ለዚህ ፕሮጀክት ስኬት የሚያስፈልጉ የ34 ፕሮጀክቶች ግብዓቶች፣ ትራንስፎርመሮች እና የተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አስቀድመው ተዘጋጅተዋል።<br>&nbsp;<br>በተጨማሪም የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ በበላይነት በሚያስተናግደውና ስትራቴጂካዊ በሆነው የኢትዮ-ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር ላይ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን የመጠቀም እቅድ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶታል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በዚህ ኮሪደር ላይ አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ለማሟላት በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህ መሆኑ የትራንስፖርትና የሎጀስቲክስ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ ከመቀነሱም በላይ፣ ሀገሪቱ ለነዳጅ ግዢ የምታወጣውን የምንዛሬ ጫና በዘላቂነት ለመታደግ ያስችላል።<br>&nbsp;<br>በጥቅሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ተጠቃሚዎችን እርካታ ለማሳደግና ሀገራዊ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ እቅዶችን ለማገዝ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው። አማራጮችን የማስፋትና መሠረተ ልማቶችን የማሟላት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የነዳጅ አልባ ትራንስፖርት ጉዞ ከዳር ለማድረስ ዋነኛ ዋስትና ነው።</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-01T15:50:00+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[EEU ዜና መጽሔት 4ኛ ሩብ ዓመት 2018 ዓ/ም]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/publication/detail/2398?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/2398</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image"><img src="/lfm/1782904105.jpg"></figure>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-01T14:10:21+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[EEU ዜና መጽሔት 3ኛ ሩብ ዓመት 2018]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/publication/detail/2397?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/2397</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image"><img src="/lfm/1782903817.jpg"></figure>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-01T14:04:02+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[በኢኤአ በየዓመቱ የሚታተም መጽሔት መስከረም 2018 ዓ.ም]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/publication/detail/1910?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/1910</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p><span style="background-color:rgb(255,255,255);color:rgb(55,65,81);"><strong>በኢኤአ በየዓመቱ የሚታተም መጽሔት መስከረም 2018 ዓ.ም</strong></span></p><p>&nbsp;</p><p><span style="background-color:rgb(255,255,255);color:rgb(55,65,81);"><strong>ተጨማሪ ይመልከቱ </strong></span><a href="https://www.eeu.gov.et/publication/detail/1909?lang=am"><span style="background-color:rgb(255,255,255);color:rgb(55,65,81);"><strong>https://www.eeu.gov.et/publication/detail/1909?lang=am</strong></span></a></p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-01T13:55:37+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ታዳሽ የሃይል ምንጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ማድረግ ይገባል]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/news/detail/2395?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/2395</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>&nbsp;</p><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃ እና ኢነርጂ ሚንስትር እና ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚደርገው የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም (NEP 3.0) ፍኖተ ካርታ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡<br>&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><figure class="image image-style-align-left"><img src="/lfm/1782805850.jpg" alt=""></figure><p>የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ይፋ በተደረገበት ወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ ለአንድ ሀገር እድገት ኢነርጂ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው ታዳሽ የሃይል ምንጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ማድረግ እንደሚገባ አስታውሰዋል።<br>&nbsp;</p><p>በሀገር አቀፍ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚያደርገው ሲሆን በወርልድ ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል። &nbsp;&nbsp;<br>&nbsp;<br>የሀገር አቀፍ የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ዋና ዓላማ በግሪድ ውስጥ እና ከግሪድ ውጪ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሠራ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች እና ከግል ሴክትር ጋር በመቀናጀት አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን እና ማሻሻል እንዲሁም የዲስትሪብዩሽን መሰረተ ልማቶችን ማሳደግ ዋነኛው ተግባሩ መሆኑ ተገልጿል፡፡<br>&nbsp;</p><p>በተጨማሪም የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት ነዋሪዎችን እና የመንግስት ተቋማትን ተጠቃሚ ማድረግ፣ ኤሌክትሪክ ተደራሽ ባልሆኑባቸው አካባቢዎች የሶላር ሲስተምን እና ታዳሽ ኃይል ምንጮችን በመጠቀም ህብረተሰቡን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማደረግ &nbsp;የሚረዳ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>በዚህ ፕሮግራም &nbsp;የግል ሴክተሩ ከግሪድ ውጪ ባሉ አካባቢዎች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማበረታታት፣ በዋናነትም የኤሌክትሪክ ጥራትን ማሻሻል፣ ንጹህ ኢነርጂ እና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እንዲሁም የትምህርት እና የጤና ተቋማትን የኢነርጂ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡<br>&nbsp;</p><p>በመረሃ ግብሩ በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመው እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈውበታል።<br>&nbsp;</p><p>​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-30T10:57:02+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞቻችን ፣]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.v1.bornatol.com/ceo-message/detail/2393?lang=am" />
            <id>https://www.v1.bornatol.com/2393</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image image_resized" style="width:75%;"><img src="/lfm/1782733028.jpg" srcset="/lfm/1782733028.jpg 800w, /lfm/1782733028.jpg 1024w, /lfm/1782733028.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት ጀርባ አጥንት የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ በአስተማማኝ፣ ተደራሽና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማቅረብ ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል። ይሁን እንጂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን መሠረታዊ ፍላጎት ቢሆንም፣ በአጠቃቀም ወቅት በሚፈጠሩ ጥንቃቄ የጎደላቸው ስህተቶችና የደህንነት መመሪያዎችን ባለመከተል ምክንያት ቀላል የማይባሉ የንብረትና የሕይወት ጉዳቶች ሊከሰቱ ይችላሉ።<br>&nbsp;</p><p>​ስለዚህ በቤትዎም ሆነ በሥራ ቦታዎ የኤሌክትሪክ ደህንነትን ማረጋገጥ ምርጫ ሳይሆን የሁላችንም የማይታለፍ ግዴታ ነው ብለን እናምናለን።<br>&nbsp;</p><p>​እንደ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ በምናከናውናቸው የኃይል ማከፋፈልና ጥገና ሥራዎች ሁሉ የሠራተኞቻችንን ብቻ ሳይሆን የክቡራን ደንበኞቻችንን እና የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ዋነኛ ኃላፊነታችን ነው።<br>&nbsp;</p><p>ከዚህም በላይ ደንበኞቻችን በየቤታቸውና በየድርጅቶቻቸው ከኤሌክትሪክ አደጋ ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማስተማርና የማስገንዘብ ሥራዎችን በልዩ ትኩረት እየሠራን እንገኛለን።<br>&nbsp;</p><p>“ቅድሚያ ለደህንነት” የሚለው መርህ በተቋማችን ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ደንበኛችን ቤትና የሥራ ቦታ የእለት ተእለት ባህል መሆን አለበት።<br>&nbsp;</p><p>​ይህንን ግንዛቤ ለማሳደግ ተቋማችን በየሦስት ወሩ የ“የሥራ ላይ ደህንነት ንቅናቄ ሳምንት” በማካሄድ፣ የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆንና የደንበኞቻችንን ደህንነት በላቀ ሁኔታ ለመጠበቅ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል። የዚህ ንቅናቄ ዋና ዓላማ እኛም ሆንን እናንተ ደንበኞቻችን ከትላንቱ በተሻለ ዛሬ ለኤሌክትሪክ ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት እንድንሰጥ ነው።<br>&nbsp;</p><p>​ይህንን ከአደጋ የፀዳ አካባቢ የመፍጠር የጋራ ግብ ለማሳካት፣ እናንተም ክቡራን ደንበኞቻችን በሚከተሉት ነጥቦች ላይ አጋር እንድትሆኑን እንጠይቃለን፦<br>&nbsp;</p><p>• በየቤታችሁና በየድርጅቶቻችሁ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መስመሮችንና ዕቃዎችን በጥንቃቄ መያዝና አደጋ እንዳያደርሱ መከታተል፣</p><p>• ​በአካባቢያችሁ የወደቁ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ወይም አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሲመለከቱ በፍጥነት ለተቋማችን ማሳወቅ፣</p><p>• ​የሚተላለፉ የኤሌክትሪክ ደህንነት የጥንቃቄ መልዕክቶችንና መመሪያዎችን በተግባር ላይ ማዋል፣</p><p>• ​ሕገ-ወጥ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዎችንና ግንኙነቶችን በመከላከል ራስዎንና ቤተሰብዎን መጠበቅ።</p><p>​ቅድሚያ ለደህንነት መስጠት ዛሬን በሰላምና በሕይወት እንድንኖር፣ ነገም በሥራችን ውጤታማ እንድንሆን የሚያስችለን መሠረታዊ ነገር ነው። ማንኛውንም የኤሌክትሪክ መሣሪያ ከመጠቀምዎ በፊት ለደህንነትዎ ቅድሚያ መስጠት የዘወትር ልማድዎ እንዲሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።<br>&nbsp;</p><p>​በመጨረሻም፣ ከአደጋ የፀዳ የኤሌክትሪክ አጠቃቀምን ማረጋገጥ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ፣ ከጎናችን ሆናችሁ አብራችሁን እንድትሠሩ በአክብሮት እጠይቃለሁ።<br><br>​አመሰግናለሁ!<br>&nbsp;</p><p>​ኢንጂነር ጌቱ ገረመው<br>ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት<br>&nbsp;</p><p>​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት<br>#ለደንበኞቻችንደህንነት<br>#ቅድሚያለደህንነት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-29T14:38:12+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
